የፌዴሬሽን ምክር ቤት የኢፌዴሪ ህገ መንግስትን ለመተርጐም ባለው ስልጣን ተጠቅሞ የሚሰጠው ውሣኔ የመጨረሻና ጉዳዩ በሚመለከተታቸው አካላት መከበርና መፈፀም ያለበት ስለመሆኑ፣ የፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ቦርድ የሚቀርብለትን አቤቱታ ህጋዊነት መርምሮ በመወሰን ሂደት ከፊል የዳኝነት ስልጣን ያለው አካል (quasi judicial body) እንደመሆኑ መጠን በህገ መንግስቱ የተጠበቁትን ፍትህ የማግኘት፣ የመሰማትና በእኩል ሚዛን የመታየት (የመዳኘት) መብት በሚያስከበር መልኩ ክርክሮችን ሊያስተናግድና ሊወስን የሚገባ ስለመሆኑ፣ የኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 62(1),37 አዋጅ ቁ. 251/93 አንቀጽ 3(1),56(1) አዋጅ ቁ. 87/86 አንቀጽ 8,9 የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 337, 336, 339