የጠፋ ዕቃን ላገኘ ወይም ሌላ ነገር ለፈፀመ ሰው ሽልማት ይሰጠዋል ተብሎ በተለጠፈ /በተነገረ/ ማስታወቂያ ወይም በአደባባይ ሊታወቅ በሚችል ሌላ አይነት ማስታወቂያ መሰረት ዕቃውን አግኝቶ የመጣ ወይም የተባለውን ሥራ የፈፀመ እንደሆነ የተስፋ ቃሉን የሰጠው ሰው የተገለፀውን ሽልማት /የገባውን ቃል/ የመፈፀም ግዴታ ያለበት ስለመሆኑ በውል የተገባ ግዴታ ፍፁም የማይቻልና የማይሞከር ነው ለማለት ተዋዋይ ወገን ብቻ ሳይሆን ማንም ሰው ሊፈጽመው የማይችለው ግዴታ መሆን ያለበት ስለመሆኑ በአንድ ከተማ የሚገኝና መጠኑ ተለይቶ የታወቀ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በሽልማት መልክ ለመስጠት በውል የተገባ ግዴታ ሊፈፀም የማይችል ነው ሊባል የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1715, 1741-1762, 1714, 1711, 1736, 1734, 1689