በባንክ በመያዣነት የተያዘ ተሽከርካሪ በሌላ በኩል የጉምሩክ ደንብ በመተላለፍ ወንጀል ባለቤቱ ጥፋተኛነቱ ተረጋግጦበት ተሽከርካሪውም በመንግስት እንዲወረስ ውሣኔ የተሰጠበት እንደሆነ በህግ ፊት ቅድሚያ ተሰጥቶት ሊፈፀም ስለሚገባው ጉዳይ በባንክ በመያዣነት የተያዘ ተሽከርካሪ ከመያዣው በኋላ በኮንትሮባንድ ወንጀል ምክንያት ለመንግስት ውርስ እንዲሆን በፍ/ቤት የመጨረሻ ፍርድ ባረፈበት ጊዜ ባለመያዣው በተሽከርካሪው ላይ ያለው የቀዳሚነት መብት እንዲሁም የውርስ ትዕዛዙ (ውሣኔው) ተፈፃሚ ሊደረጉ ስለሚችልበት አግባብ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ 2828, 2857(1), 3059 አዋጅ ቁ. 97/90 አንቀጽ 3 የወንጀል ህግ አንቀጽ 98(1)