common property

  • አንድ ባለሙያ በአሠሪው ቁጥጥር ሳይሆን በራሱ የሙያ ኃላፊነት የሙያ አገልግሎት ለመስጠት ከአንድ አሠሪ ጋር ውል ሲኖረው ጉዳዩ የሚገዛው በአሠሪና ሠራተኛ ህግ ስላለመሆኑ፣

    -ከአንድ ባለሙያ ጋር የሙያ ግልጋሎት ውል ያለው አሠሪ ውሉን በማናቸውም ጊዜ ማፍረስ ሥለመቻሉ፣

    አንድ አሠሪ ለሙከራ የቀጠረውን ሠራተኛ በቀጠረው በ46ኛው ቀን ለስራው ብቁ አይደለም ብሎ የስንብት ደብዳቤ ቢጽፍለት ድርጊቱ ህገ ወጥ ነው ሊባል የማይችል ስለመሆኑ፣

     

    አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ

    ...
  • ጋብቻ በሁኔታ ፈርሷል ሊባልባቸው ስለሚችሉባቸው ሁኔታዎች ጋብቻ በሁኔታ ፈርሷል ተብሎ ከሚታሰብበት ጊዜ አንስቶ በአስር ዓመት ጊዜ ውስጥ የንብረት ክፍፍል ጥያቄ ካልቀረበ በይርጋ የሚታገድ ስለመሆኑ

     

    የሰ/መ/ቁ.102662

    የካቲት 15 ቀን 2008 ዓ/ም

    ዳኞች፡-አልማው ወሌ ዓሊ መሐመድ ተኽሊት ይመሰል እንዳሻው አዳነ ቀነዓ ቂጣታ

    አመልካች፡- ወ/ሮ አልማዝ ለሼ- ጠበቃ ኤርሚያስ ደስታ ቀረቡ፡፡ ተጠሪ፡- አቶ በቀለ በላቸው- ወኪል 

    ...
  • በተሻሻለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቤተሰብ ህግ መሰረት ባልና ሚስት የጋራ ንብረታቸውን እኩል የማስተዳደር መብት ያላቸውና የጋራ ስምምነት ሳይኖር ንብረትን ለሌላ 3ኛ ወገን በአንደኛው ተጋቢ ፍቃድ ብቻ የተላለፈ ከሆነና ይህንን ስምምነቱን ያልሰጠው ተጋቢ በህጉ በተፈቀደለት ጊዜ ገደብ ውስጥ የይፍረስልኝ ጥያቄውን ካላቀረበ የተፈፀመው ተግባር እንደፀና የሚቆይ ስለመሆኑ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 68፣69

     

    የሰ/መ/ቁ. 103721

    የካቲት 03 ቀን 2008 ዓ.ም

     

     

    አንድ ጋብቻ ሲፈርስ ንብረት ክፍፍልን በሚመለከት በእርቅ ውል ስምምነት በሽማግሌ የተደረገው እርቅ በፍ/ቤት ተመዝግቦ ከተዘጋ በኋላ እንደገና እንደ ባልና ሚስት አብረን እየኖርን ስለነበር በድጋሚ የንብረት ክፍፍል ይደረግ የሚል ጥያቄ አግባብነት ያለው ስላለመሆኑ፣

     

    የሰ/መ/ቁ. 105054

    ታህሳስ 22 ቀን 2008ዓ/ም

    ዳኞች፡- ተሻገር ገ/ስላሴ

     

    ባል ወይም ሚስት የጡረታ አበል ተጠቃሚ ሆነው ባሉበት ፍቺ ቢከሰት የጡረታ መብት ተጠቃሚ የሆነው ባል ወይም ሚስት የጡረታ አበል ለባል ወይም ለሚስት ሊያካፍል የሚገባ ስላለመሆኑ ፣ የመንግስት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 345/95 አንቀጽ 35

    Download Cassation Decision

  • የገጠር መሬት እንደሌላው ንብረት በመቁጠር ከቤተሰብ ህጉ አንጻር የሚታይ ስላለመሆኑ ፣ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በአንድ ተጋቢ ስም ተዘጋጅቶ ከተሰጠ በኋላ ጋብቻ ቢፈፀምና ተጋቢዎቹ መሬቱን የጋራ ለማድረግ ሊስማሙ የሚችሉ ስለመሆኑ፣ የአማራ ክልል የገጠር መሬት አጠቃቀም አዋጅ ቁ. 133/1999 አንቀጽ 24/3/ ደንብ ቁ. 151/1999 አንቀጽ 20/6/

    Download Cassation Decision

  • የመጀመሪያ ሚስት በንብረትዋ ላይ ስምምነት ባላደረገችበት ፤ባል ሁለተኛ ሚስት ሲያገባ መቃወሚያ አላቀረበችም በማለት በንብረትዋ ላይም ስምምነት አድርጋለች በማለት በመደምደም ፤ሁለተኛ ሚስት እኩል እንድትካፈል በማለት የሚሰጥ ውሳኔ ህጋዊ ስላለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • የባልና ሚስት የጋራ ንብረት ነው የተባለ ንብረትን አፈፃፀምን በተመለከተ የንብረቱ ሕጋዊነት ላይ የሚመለከተው አስተዳደር አካል አግባብ ያለው ውሣኔ እስኪሰጥ ድረስ መሸጥ መለወጥ ባይቻልም ባለበት ሁኔታ የግራ ቀኙን እኩል ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ አግባብ በጋራ የሚያስተዳድሩበት ወይም ተከፋፍለው የሚጠቀሙበት ወይም አከራይተው ጥቅሙን እኩል የሚከፋፈሉበት ሁኔታ መመቻቸት ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ 386/2/

    Download Cassation Decision

  • ባ ል እና ሚስት በጋራ ሲጠቀሙበት የነበረ መሬት ጋብቻው በአንደኛው ተጋቢ ሞት የተቋረጠ ቢሆንም ሌላኛው ተጋቢ በሌላ ህጋዊ ምክንያት መብቱ እስካልተቋረጠ ድረስ ይዞታው በስሙ ተመዝግቦ ደብተር ለማግኘት እና በይዞታው ለመጠቀም የሚችል ስለመሆኑ፣ ሴቶች መሬትን በመጠቀም፤በማስተላለፍ፤በማስተዳደርና በመቆጣጠር ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት ያላቸዉ ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕ/መ አንቀጽ 35/7/፣ የኦሮሚያ የገጠር መሬት አዋጅ ቁ. 130/99 አንቀጽ 6/3/ እና ደንብ ቁጥር 151/2005 አንቀጽ 15

    Download Cassation Decision

  • በባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ክርክር ወቅት ድብቅ የጦር መሳሪያ መኖሩ እስከተረጋገጠ ድረስ በሕግ አግባብ ስልጣን ባለዉ አካል አለመመዝገቡ መሳሪያዉ የለም የሚያስብል ሳይሆን የኢኮኖሚ ጥቅም ያለዉ እና ባልና ሚስት በትዳር እያሉ ያፈሩት እስከሆነ ድረስ ከሚመለከተዉ አካል ተመዝግቦ መሳሪያዉን ለመያዝ ፈቃድ አለመሰጠቱ፣ የተጋቢዎቹ የጋራ ሀብት እንዳይሆን የማያደርገዉ ስለመሆኑ 
    የአማራ ክልል የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 79/1995 አንቀጽ 73 (1) እና 101

    Download

     

  • ጋብቻ በፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ በንብረት ክርክር ወቅት የግል ዕዳ ነዉ ተብሎ ውሳኔ ያገኘ ዕዳ ፍ/ቤት ቀርቦ ባልተለወጠበት ሁኔታ በባለዕዳው ተጋቢ በኩል ለመጣው እዳ ሌላኛው ተጋቢ ተጠያቂነት የሌለበት ስለመሆኑ 
    የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 34 (1)፣ የፌደራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 57፣ 70፣ 71፣ 89 እና 93 

    Download

  • የፍ/ብ/ህ/ቁ. 658 ተጋቢ ወገን ከሦስተኛ ወገን ጋር ያደረገውን ውል ለማፍረስ ምክንያት ስላለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 658, 686

    Cassation Decision no. 28663

  • ከጋብቻ በፊት የግል የነበረን ንብረት መነሻ በማድረግ በጋብቻ ጊዜ በግብይት የተገኘ ንብረት የግል ሆኖ ሊቀጥል የሚችለው በፍ/ቤት ቀርቦ የፀደቀ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 58(2) 57 62(2)

    Download Cassation Decision

  • የአንደኛው ተጋቢ ስምምነት ሣይኖር የጋራ የሆነ የማይንቀሣቀስ ንብረት በሌለኛው ተጋቢ የተሸጠ እንደሆን ስምምነቱን ያልሰጠው ተጋቢ ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ 6 ወር ውስጥ እንዲሁም በማናቸውም ሁኔታ ደግሞ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ ለመጠየት ስለመቻሉ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 69(2)

    Download Cassation Decision

  • በጋብቻ ውል ላይ ባልና ሚስት “መተዳደሪያችን” ነው በሚል ያመለከቷቸው ንብረቶች የጋራ ንብረት ተደርገው የሚቆጠሩ ስለመሆናቸው

    Download Cassation Decision

  • አንድ ወንድ ሁለት ሚስቶች ጋር ተጋብቶ በሚገኝ ጊዜ የንብረት ክፍፍል ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የፌዴራል የተሻቫለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ. 213/92 አንቀጽ 102(1),86(1),62(1),63(1) የአማራ ብ/ክ/መ/የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 113(1),97(1),73(1),74(1)

    Download Cassation Decision

  • በባልና ሚስት የጋራ ንብረት ላይ የተደረገ የሽያጭ ውል በሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ አለመፍረሱ ስለሚያስከትለው ውጤት

    Download Cassation Decision

  • ከኮንዶሚኒየም ቤት ባለቤትነት ጋር በተያያዘ ከጋብቻ በፊት በአንደኛ ተጋቢ በተደረገ ምዝገባ የተነሣ የቤት ዕጣው የወጣው ብሎም የቤት ሽያጭ ውል የተደረገው በጋብቻ ወቅት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ለቤቱ መገኘት ምክንያት የሆነው ተጋቢ ቤቱ የግል መሆን አለበት በሚል የሚያቀርበው ክርክር ተቀባይነት የሌለው ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 62(2)

    Download Cassation Decision

  • የጋብቻ ፍቺን በተመለከተ በፍ/ቤት የተሰጠ ውሣኔ ከሌለ በስተቀር የባልና ሚስት የጋራ ንብረትን አስመልክቶ የፍቺ ውጤት የሆነውን የክፍፍል ጥያቄ በፍ/ቤት ማቅረብ አይቻልም ለማለት የሚያስችል የህግ አግባብ የሌለ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 76

    Download Cassation Decision

Page 2 of 3