federal proclamations, regulations, directives, regional constitutions and laws.
You can search cases by number, volume, subject matter
Training and teaching materials, articles, legal forms, links to resources...
ከጋብቻ በፊት የግል የነበረ ንብረት በተጋቢዎች የጋብቻ ውል መነሻነት የጋራ ሊሆን የሚችል ስለመሆኑ
Download Cassation Decision
የጉዲፈቻ ስምምነት የሕፃናትን ጥቅምት ለማስጠበቅ ሲባል ሊፈርስ የሚችል ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 195(2)
ከውርስ ሃብት ክፍፍል ጋር በተያያዘ ተጠቃሚው በኢንሹራንስ ውል ላይ ባልተገለፀበት ጊዜ የሟች ባል ወይም ሚስት የኢንሹራንስ ገንዘቡን ከወራሾች ጋር ሊካፈሉ የሚችሉበት አግባብ የንግድ ህግ ቁጥር 705 701(1)(ሀ) የፍ/ብ/ህ/ቁ. 827
አባትነት በህግ አግባብ ሊታወቅ የሚችልባቸው ሁኔታዎች የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 126 1(1) (2),128(1) 130(2) 125 106(1), የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 35(2)
በትዳር ወቅት የተወሰደ ብድር የአንደኛው ተጋቢ ፈቃድ የሌለበት ቢሆንም ፈቃዱን ያልሰጠው ተጋቢ የብድር ስምምነቱ እንዲፈርስ ያላደረገ እንደሆነ ወይም ደግሞ ለትዳር ጥቅም አለመዋሉን ማስረዳት ያልቻለ ከሆነ ለትዳር ጥቅም እንደዋለ የህግ ግምት የሚወሰድ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 68(መ)
አንድ ወንድ ሁለት ሚስቶች ጋር ተጋብቶ በሚገኝ ጊዜ የንብረት ክፍፍል ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የፌዴራል የተሻቫለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ. 213/92 አንቀጽ 102(1),86(1),62(1),63(1) የአማራ ብ/ክ/መ/የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 113(1),97(1),73(1),74(1)
የልጆች ቀለብ አከፋፈል ሁኔታ ጋር በተያያዘ ክፍያ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችልበት አግባብ
ሞግዚት የሆነ ሰው በሞግዚትነት የሚያስተዳድራቸውን ልጆች ሀብት የሆነን ንብረት ለልጆቹ መልካም አስተዳደግ ሲል ሊሸጠው የሚችል ስለመሆኑ የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ ቤተሰብ ህግ አንቀፅ 292
በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር ሁኔታ ስለመኖሩ ለማስረዳት የሚችሉት በግንኙነቱ ውስጥ ያሉት ሰዎች ብቻ ናቸው ለማለት የሚያስችል የሕግ መሰረት የሌለ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 98,99,106
የንግድ አሰራር አጣሪ ኮሚሽን ያልተገባ የንግድ ውድድርን በተመለከተ የሚነሳ ክርክርን የመዳኘት ስልጣን ያለው ስለመሆኑ የንግድ አሰራር አጣሪ ኮሚሽን ተግባርና ኃላፊነት አዋጅ ቁ. 329/95 አንቀጽ 10/2/ /ሀ/, 3, 15 አዋጅ ቁ. 501/98 አንቀጽ 49 አዋጅ ቁ. 67/89 አንቀጽ 46 አዋጅ ቁ. 361/95 አንቀጽ 41/2/, 52
በባልና ሚስት የጋራ ንብረት ላይ የተደረገ የሽያጭ ውል በሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ አለመፍረሱ ስለሚያስከትለው ውጤት
ከኮንዶሚኒየም ቤት ባለቤትነት ጋር በተያያዘ ከጋብቻ በፊት በአንደኛ ተጋቢ በተደረገ ምዝገባ የተነሣ የቤት ዕጣው የወጣው ብሎም የቤት ሽያጭ ውል የተደረገው በጋብቻ ወቅት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ለቤቱ መገኘት ምክንያት የሆነው ተጋቢ ቤቱ የግል መሆን አለበት በሚል የሚያቀርበው ክርክር ተቀባይነት የሌለው ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 62(2)
የጉዲፈቻ ውል እንዲፈርስ ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 195(1) (2)
የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት በሚሰጣቸው ውሣኔዎች ላይ ቅሬታ አለኝ የሚል ወገን ያለው መብት ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ይግባኝ ማቅረብ ነው እንጂ የቀጥታ ክስ ማቅረብ ስላለመሆኑ የፌ/ጠፍ/ቤት ሦስት ዳኞች በሚሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው ትዕዛዝ /ውሣኔ/ አስገዳጅ ስላለመሆኑ አዋጅ ቁ. 454/97 አንቀጽ 2/1/ አዋጅ ቁ. 25/88 አዋጅ ቁ. 501/98 አንቀጽ 6, 17, 36, 49 አዋጅ ቁ. 320/95 አዋጅ ቁ. 410/96
የጋብቻ ፍቺን በተመለከተ በፍ/ቤት የተሰጠ ውሣኔ ከሌለ በስተቀር የባልና ሚስት የጋራ ንብረትን አስመልክቶ የፍቺ ውጤት የሆነውን የክፍፍል ጥያቄ በፍ/ቤት ማቅረብ አይቻልም ለማለት የሚያስችል የህግ አግባብ የሌለ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 76
በተከሳሽ ወይም ከሳሽ ሞት ምክንያት በፍ/ቤት በመካሄድ ላይ የነበረ ክርክር በተቋረጠ ጊዜ ክርክሩ በወራሾች አማካኝነት ሊቀጥል የሚችልበት ሁኔታና በህጉ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ተፈፃሚ ሊሆን የሚችልበት አግባብ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.49(1), 55(2)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤቶች ንብረትነታቸው የከተማው አስተዳደር ለመሆናቸው ክርክር በማይቀርብባቸው ቤቶች ላይ የሚነሱ የይዞታ፣ የኪራይ እና ሌሎች ክርክሮችን አይተው ለመወሰን ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ የሁከት ይወገድልኝ ክስ ከከተማው መሪ ፕላን ጋር እስካልተያያዘ ድረስ በከተማው ፍ/ቤቶች የሥረ ነገር ስልጣን ሥር የሚወድቅ ስላለመሆኑ የሥረ ነገር ስልጣን ሳይኖር የሚሰጥ ፍርድ እንዳልተሰጠ የሚቆጠርና ህጋዊ አስገዳጅነት የሌለው ስለመሆኑ ከቤት ይዞታ ጋር በተገናኘ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤቶች የተሰጣቸው ስልጣን ሁከት ይወገድልኝ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄን መሰረት ባደረገ መልኩ ሲቀርብ ስላለመሆኑ
ባንኮች ላበደሩት ገንዘብ በመያዣነት የያዙትን የማይንቀሳቀስ ንብረት በዕዳ መክፈያነት በሐራጅ ለመሸጥ የተሰጣቸውን ስልጣን በተግባር ሲያውሉ ህግን በመተላለፍ በባለዕዳው ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ተጠያቂነት ያለባቸው ስለመሆኑ በመያዣነት የተያዘውን ንብረት በሐራጅ ለመሸጠም የፍርድ ቤት ውሣኔ ወይም ፈቃድ የማያስፈልጋቸው ስለመሆኑ አበዳሪ የሆነ ባንክ በአዋጅ ቁ. 97/90 የተሰጠውን ስልጣን /መብት/ ትቷል (waive) ሊባል ስለሚችልበት አግባብ
ከባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ጋር በተገናኘ በአንደኛው ተጋቢ በውርስ የተገኙ ንብረቶች (ሀብቶች) ለልማት በሚል በመፍረሳቸው የተገኘ የካሳ ክፍያ በግብይት እንደተገኘ ተቆጥሮ የግል ስለመሆኑ በፍ/ቤት አልተረጋገጠም በሚል እንደ የጋራ ሀብት ሊቆጠር የማይችል ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 58, 57
በጋብቻ ተሳስረው የነበሩ ሰዎች ግንኙነታቸው እስካልተቋረጠ ድረስ ለረጅም ጊዜ ተለያይተው በመኖራቸው ብቻ በመካከላቸው ያለው የትዳር ግንኙነት ፈርሷል ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣
Page 6 of 8