103721 family law/ administration of common property

በተሻሻለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቤተሰብ ህግ መሰረት ባልና ሚስት የጋራ ንብረታቸውን እኩል የማስተዳደር መብት ያላቸውና የጋራ ስምምነት ሳይኖር ንብረትን ለሌላ 3ኛ ወገን በአንደኛው ተጋቢ ፍቃድ ብቻ የተላለፈ ከሆነና ይህንን ስምምነቱን ያልሰጠው ተጋቢ በህጉ በተፈቀደለት ጊዜ ገደብ ውስጥ የይፍረስልኝ ጥያቄውን ካላቀረበ የተፈፀመው ተግባር እንደፀና የሚቆይ ስለመሆኑ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 68፣69

 

የሰ/መ/ቁ. 103721

የካቲት 03 ቀን 2008 ዓ.ም

 

 

ዳኞች፡- ተሻገር ገ/ስላሴ

ሙስጠፋ አህመድ ተፈሪ ገብሩ

ሸምሱ ሲርጋጋ አብርሃ መሰለ

 

አመልካች፡-  ወ/ሮ ሰሚራ ጀማል ከጠበቃ ሰለሞን ታደሰ ቀረቡ ተጠሪ፡- 1ኛ. አቶ ጀማል እንዲሪስ ከጠበቃ መሰረት ስዩም ጋር ቀረቡ

2ኛ. ወ/ሮ ሉላ አረፈ አልቀረቡም

3ኛ.አቶ ሀጎስ አብዱራህማን በመዝገብ ቤት በኩል እንዲሰሙ ተናግሯል፡፡

መዝገቡ ተመርምሮ ተገቢውን ዳኝነት ለመስጠት ለየካቲት 01 ቀን 2008 ዓ/ም ቀጠሮ የያዘ ሲሆን በዚህም መሰረት መዝገቡን መርምረን በአዳሪ በዚሁ እለት የሚከተለውን  ፍርድ ሰጥተናል፡፡

 ፍ ር ድ

ይህ የሰበር ጉዳይ በአሁን አመልካችና 1ኛ ተጠሪ መካከል የነበረው ጋብቻ በፍ/ቤት የፍቺ ውሳኔ መሰረት መፍረሱን ተከትሉ በአሁን አመልካች የጋራ ንብረት ድርሻ ጥያቄ መነሻ የስር ፍ/ቤቶች የጋብቻ ውጤት በሆነው የንብረት ክርክር ላይ የሰጡትን ዳኝነት በዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ክርክር ካስነሳው የውሳኔ ክፍል አንፃር ተመልክቶ የውሳኔውን አግባብነት ከግራ ቀኙና ክርክሩ የሚመለከተው ሆኖ የተገኘው 3ኛ ተጠሪም ካቀረቡት ክርክር ጋር በማገናዘብ አስፈላጊውን ዳኝነት ለመስጠት በሚል የቀረበ ነው፡፡

 

የጉዳዩም አመጣጥ ባጭሩ እንደሚከተለው ነው በአሁን አመልካች እና 1ኛ ተጠሪ መካከል ሚያዚያ 21  ቀን 1987 ዓ/ም ተደርጎ የነበረው ጋብቻ ግንቦት 24 ቀን 2003 ዓ/ም  በፍ/ቤት የፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተክትሎ የአሁን ተጠሪ ሀምሌ 27 ቀን 2003 ዓ/ም ተሻሽሎ ባቀረቡ ማመልከቻ የጋራ ንብረት ናቸው ያሏቸውን ናቸው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቶች በመዘርዘር ድርሻቸው ተለይቶ ይወሰንላቸው ዘንድ ተገቢ የነበሩትን የአሁን 1ኛ ተጠሪን እና የ1ኛ ተጠሪ ሌላ ሚስት የሆነችን የአሁን 2ኛ ተጠሪን በተከሳሽነት ላይ ደመወዝ በዚሁ የጋብቻ ውጤት በሆነው የንብረት ድርሻ ጥያቄ ላይ፣ እንደዚህም 1ኛ ተጠሪ የጋራ ንብረትን ሲያስተዳድር የደረሰው፣  ጉዳት ሲታወቅ በኃላ ተገቢውን የካሳ ለአመልካች እንዳይከፍል ይወሰንልኝ   በማለት


ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ እንደክርክራቸው ያስረዳልናል ያሏቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃም አያይዘው አቀርበናል፡፡

 

የአሁን 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎች የጋራ ንብረት ናቸው በሚል በአሁን አመልካች የክስ ማመልከቻ ላይ ከተዘረዘሩት ንብረቶች የጋራ ንብረት የሆኑትን በማመን፣ በጋራ ሀብትነት የማይታወቁትን፤ የሚያገኙትን ደግሞ በመካድ በአመልካች ክስ በተዘረዘረው የንብረት ዝርዝር አንፃር መልስ የሰጡ ሲሆን፤ በንብረት አስተዳደር ረገድ ያደረስኩት ጉዳት የሌላ በመሆኑ የሰጠው  ጥያቄ አይመለከተኝም በማለት ክርክራቸውን አቅርቧዋል፡፡ ለክርክሩም ድጋፍ ያላቸውን ማስረጃዎች አያይዘው አቅርበዋል፡፡

 

የአሁን 3ኛ ተጠሪም የጋራ ንብረት ነው በሚል በአሁን አመልካች ከተጠቀሱት ንብረቶችና መካከል በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍል ከተማ ወረዳ 3 ክልል በቤት  ቁጥር 2545  የሚታወቀውን ቤት በውል አዋዋዩ ክፍል ዘንድ ጂ. ኤስ. ኤ.ጄኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ከተባለው ድርጅት የገዙት ስለሆነ የአመልካችን ጥያቄ ውድቅ ለማድረግ ይወሰንልኝ በማለት በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብተውም ተከራክረዋል፡፡ ለዚህም ክርክራቸው ለማስረጃነት ሰነዶችን እንዳቀረበም የመዝገቡ መልሰን ያስረዳል፡፡

 

እኚሁ ጣልቃ ገብ ያቀረቡትን ክርክር አስመልክቶ የአሁን አመልካች ጣልቃገብ ፍ/ቤቱ በንብረቱ ላይ የእግድ ትእዛዝ በሰጠበት ንብረት ላይ ግዥ የፈጸሙ ስለሆነ የሽያጭ ውሉ ከጅምሩ ፈራሽ ስለሆነ ጥያቄው ተቀባይነት የለውም በማለት ተከራክረዋል፡፡

 

የአሁን 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎች ይህንኑ በቁጥር 2545 ተመዝግቦ የሚታወቀውን ቤት አስመልክቶ ንብረቱ በማናቸውም ስም ተመዝግቦ የሚታወቅ የጋራ ንብረት ባለመሆኑ እንጂ የጋራ ንብረት ተቆጥሮ መቅረቡ ተገቢ አይደለም በማለት አመልካች ባቀረቡት ክስ ቀጥተኛ መልስ የሰጡ ከመሆኑም በላይ በጣልቃ ገብ በኩል የቀረበው ክርክር አስመልክቶ ደግሞ ተቃውሞ የሌለባቸው መሆኑን ገልጸናል፡፡

 

ሁሉም ወገኖች ከላይ ባጭሩ ለይዞታ ደረጃ የተገለጸውን የጹሁፍ ክርክር ካደረጉ በኋላ ለጉዳዩም ላይ የቃል ክርክር እንዳደረጉ መዝገቡ ያስረዳል፡፡

 

የስር ፍ/ቤትም ከግራ ቀኙ ክርክር በመነሳት በአከራካሪነታቸው በጭብጥነት ተይዘው ከማስረጃ አንፃር ለማየት ዳኝነት ያስፈልጋቸዋል፡፡ በማለት ከሙግት ደረጃ ደርሶ ለማስረጃ ሰምቶ ዳኝነት ካሳረፈባቸው ንብረቶች መካከል በአከራካሪያቸው ከዚህ ሰበር ደረጃ ዘልቀው ከደረሱት መካከል አንዱ በቤት ቁጥር 2545 የተመዘገበውን ቤት አስመልክቶ


የአሁን አመልካች በጋብቻ ዘንድ የተፈራውን ይህንኑ ንብረት ከእኔ ለማሸሽ ሲል ያለ እኔ ፈቃድ ጀ. ኤስ.ኤ አጄኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ወደ ተባለው ድርጅት በመዋጨነት አስገምቶ አሽሽቶ የሰጠ በመሆኑ፤ እንዲሁም ይህን ንብረት የአሁን 3ኛ ተጠሪ ፍ/ቤቱ በንብረቱ ላይ የእግድ ትእዛዝ ከተሰጠበት በኋላ እንዲገዙት የተደረገ ስለሆነ ንብረቱ የጋራ ሀብት መሆኑ ታውቆ በድርሻዬ ልከፍል ይገባል በማለት የተከራከሩ ቢሆንም በኢፊድሪ የፍትህ ሚንስተር የሰነዶች ማረጋገጫና ከዘገባ ጽ/ቤት በቀን 10/3/2002 ዓ/ም በተፈረመ የጂ ኤስ ኤ ጄነራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር የመመስረቻ ጽሁፍ ይዘው በቤት ቁጥር 2545 ተመዝግቦ የሚታወቀው  በ1ኛ ተጠሪ  አማካኝነት በመጭነት  የተመዘገበ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

 

ሚያዚያ 16 ቀን 2002 ዓ/ም በተካሄደ የጂ ኤስ ኤ.ኤጀኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ለሂሳብ 1ኛ ተጠሪ በማህበሩ የየራሳቸውን አክስዮን በብር 240,000.00 /ሁለት መቶ አርባ ሺህ ብር/ ሽጠው የተሰራበት መሆኑ በኢፈደሪ የፍትህ ሚኒስቴር ማስረጃ ማረጋገጫ ምዝገባ ጽ/ቤት ማህተም በተረጋጠ ሰነድ ተረጋግጧል ጂ. ኤስ ጄኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/ የግል ማህበር ግንቦት 17 ቀን 2003 ዓ/ም በተፃፈና በሰነዶች ማረጋገጫና መዝገብ ጽ/ቤት በተመዘገበ የሽያጭ ውል ይህንኑ የቤት ቁጥር 2545 የሆነው በብር 240,000.00 /ሁለት መቶ አርባ ሺህ ብር/ ለጣልቃ ገብ ለአሁን 3ኛ ተጠሪ አብዱራህማን አህመድ የተሸጠ ስለመሆኑም በጣልቃ ገብ አማካኝነት በቀረበው የጽሁፍ ማስረጃ ተረጋግጧ በመሆኑም ይኸው ቤት ከ1ኛ ተጠሪ እጅ ሙሉ በሙሉ ወጥቶ በጂ ኤስ. ኤ.ተራ ደንብ ኃ/የተ/የግል ማህበር ተጠቃሎ ተላልፏል የተስፋፋውም የአመልካችና 1ኛ ተጠሪ ጋብቻ እንዳይፈርስ የፍቺ ጥያቄ ለመቅረቡ በፊት እና ለፍ/ቤት የእግድ ትእዛዝ በፊት ስለመሆኑ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡

 

የጋራ የሆነውን ንብረት ያለ ሁለተኛው ተጋቢ ፈቃድ በአንደኛው ተጋቢ አማካኝነት ተላልፎ የተገኘ እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀፅ 68/ሀ/ እና 69 እንደተደነገገው ፈቅደን ባልሰጠው ተጋቢ ጥያቄ መሰረት ንብረቱ የተላለፈበት ግዴታ እንዲፈርስ ካልተደረገ በቀር በተፈጸፀመው የንብረት ማስተላለፍ ስምምነት ውስጥ ተጋቢዎች እንደታሰበው ግምት እንደሚሰጡ ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረት አመልካች በዚህ በመ/ቁ 2545 የተደረገውን የሽያጭ ስምምነት  በመቃወም በፍ/ቤት ጥያቄ አቅርበው ያስወሰኑት የለም፡፡ ስለሆነም ንብረቱን ከእኔ ለማሸሽ ሲል ለኢኤስኤ ትሬድንግ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር በመውጫ ሰጥቷል የፍ/ቤቱን ዕግድ በመጣስ  ሸጦታል በማለት ያቀረቡት ክርክር ራሱ ችሎ መቅረብ የነበረበት ክርክር እንጅ በዚህ አሁን በቀረበው ክርክር ሊታይ የማይችል ከመሆኑም በላይ ንብረቱ ወደ ማህበሩ የተዛወረው በአመልካች በኩል የፍቺ ጥያቄ ለመቅረብና የዕግድ ትዕዛዝ ከመተላለፉ በፊት ስለሆነ የመ/ቁጥር  2545 የሚታወቀው ቤት የአመልካችና የተጠሪዎች የጋራ ሀብት ሳይሆን ጣልቃ ገብ በግዥ ያገኙት ንብረት ነው በማለት ወስኗል፡፡ እንዲሁም በዘምዘም ባንክ አ/ማህበር በተጠሪዎች ስም  የአከሲዮን


ድርሻ የለም፣ በባንክ ስማችን የተቀመጠ ገንዘብ የለም በማለት ተጠሪዎች ቢከራከሩም ፍ/ቤቱ ስላቀረበው ማስረጃ ጭምር የተረጋገጠ ሆኖ ተገኝቷል በማለት ተረጋግጧል ባለው የገንዘብ መጠን መሰረት የአሁን አመልካች ድርሻ እንዳላቸው ገልፆ ዳኝነት ሰጥቶበታል በሌላ በኩል ጋብቻው ፀንቶ በነበረበት ወቅት ንብረት በማስተዳደር በኩል የፈፀሙት ጉድለት ያለመሆኑ ያለ መሆኑ ተጣርቶ ከተረጋገጠ በኋላ ለማ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል፡፡ ይሁን እንጅ ተጋቢዎች በጋብቻቸው ዘመን የጋራ ንብረታቸውን በጋራ እንዲያስተዳድሩ በሕጉ ግምት የሚወስድ ሲሆን ይህን ግምት ማፍረስ የሚቻለው አንደኛው ተጋቢ የሌለውን መብት የሚጎዳ ተግባር ፈፅሞ ስለመገኘቱ የማረጋገጥ ማስረጃ የቀረበ እንደሆነ በሕጉ አንቀፅ 87 ተደንግጓል 1ኛ ተጠሪ  ንብረት ሲያስተዳድሩ ፈፀሙ በሚል በማስረጃ የተረጋገጠና ተለይቶ የታወቀ ጉድለት ያልተገኘ በመሆኑ ፍ/ቤቱ ጥያቄውን አልተቀበለውም የሚለውን ውሳኔ ሰጥቶበታል፡፡ፍ/ቤቱ ለሰጠው ዳኝነት በምክንያትነት ያሰፈረውን ሐተታ እና የሰጠውን የዳኝነት ዓይነት ከዚህ በላይ ባሰፈረው አኳኋን በሰጠው የፍርድ ክፍል ላይ ከገለፀው በኋላ በፍርድ መሰረት የተረጋገጠውንና ሊረጋገጥ ያልቻለውን ምስክር አስመልክቶ የፍርድ ተከታይ በሆነው የውሳኔ ክፍል ላይ

 

በቂርቆስ ክ/ከተማ በቀሌ 02/03 ክልል በቤት ቁጥር 297 ተመዝግቦ የሚገኘውን ቤት በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የሚገኘውን ቤት አመልካችና ተጠሪዎች በጋራ ያፈሩት ንብረቶች ስለሆነ የክፍፍሉንም መንገድና ስልት ከመጥቀስ ጋር ሶስቱም እኩል እንዲከፈሉ በን/ስ/ላፍ/ክፍለ ከተማ በመ/ቁጥር 2545 የግልግል ሀብት ነው፤

 

1ኛ ተጠሪ በቴክኖሎጅ ሲስተም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ያላቸውን ሸር፣ በፒስ ደልለን ኃ/የተ/የማህበር ውስጥ ያለው ሸር 2ኛ ተጠሪ በዘምዘም ባንክ አ/ማህበር ያላቸው በሁለተኛ ተጠሪ ስም በዳሽን ባንክ ስለ አካባቢ ቅርንጫፍ በ1ኛ ተጠሪ ስም በወጋገን ባንክ ተ/ኃይማኖት ቅርንጫፍ በ1ኛ ተጠሪ ስም በዳሽን ባንክ ስለ አካባቢ ያስቀመጠውን ገንዘብ ከእነ መጠኑ በመግለፅ ሶስቱም እኩል እንዲካፈሉ በማለት በኮ/መ/ቁ 61875 በቀን 13/10/2004 ዓ.ም ወስኖ ግራ ቀኙን አሰናብቷል፡፡

 

በዚህ ውሳኔ የአሁን አመልካች ቅር ተሰኝተው ባቀረቡት የይግባኝ ቅሬታ መነሻ ይግባኝ ሰሚው ከፍተኛ ፍ/ቤት በኮ/መ/ቁ 125893 ሁሉንም ወገኖች ከክርክር በኋላ

 

የቤት ቁጥር 2545 አስመልክቶ የቀረበውን ጉዳይ በሚመለከት በዚሁ ቤት ላይ የስር ፍ/ቤት የካቲት 16/2003 ዓ.ም የዕግድ ትዕዛዝ ከመስጠቱ በፊት ቤቱ በ1ኛ አማካኝነት በመውጫነት ወደ ጅ.ኤስ.ኤ ጀኔራል ትሬድግግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ገብቶ የነበረ እና 1ኛ ተጠሪ በማህበሩ ውስጥ የነበራቸውን 4127/4/ለ/2002 በቀን 12/9/2002 መተላለፉን የሰነዶች ማረጋገጫ ፅ/ቤት ለስር ፍ/ቤት በቀን 20/4/2004 ዓ.ም ከላከው ማስረጃ አረጋግጧል፡፡ እንዲሁም የዚሁ ቤት ስመ-


ሀብትነት ወደ ጅኤስኤ ጀኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በቀን 04/8/2002 በቁጥር ን/ስ/ቀ/05/83/3805/02 የተላለፈ ስለመሆኑ የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ መሬት አስተደደርና ግንባታ ፅ/ቤት የካቲት 14 ቀን 2003 ዓ.ም በተፃፈና ለስር ፍ/ቤት ከላከው ሰነድ ተረጋግጧል፡፡

 

ቤቱ ወደ ሶስተኛ ወገን በተላለፈበት ጊዜ ግንቦት 1/2002 ዓ.ም ግራ ቀኙ በጋብቻ ውስጥ የነበሩ ስለመሆኑ የስር ፍ/ቤት ግንቦት 24 ቀን 2002 ዓ.ም የሰጠው የፍቺ ውሳኔ ያረጋግጣል፡፡ በመሆኑም ይኽው ንብረት በጋብቻ ጊዜ ወደ ሶስተኛ ወገን ሲተላለፍ መተላለፉን አላወቀም ነበር የሚሉ ሲሆን አሁን ለዚህ ችሎት ውሉ እንዲፈርስ ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ጥያቄ አቅርበው እየተከራከሩ እንደሚገኙ በገለፁት መልኩ ይኽው ውል በማስፈረስ መብታቸውን ከሚያስከብሩ በቀር በጠየቁት ዳኝነት አኳኋን ሊስተናገድ የሚችል አይደለም በማለት የስር ፍ/ቤትን ውሳኔ ሲያፀናው በ1ኛ ተጠሪ እና በ2ኛ ተጠሪ ስም የሚገኘውን የሼር ሀብት መጠንን በሚመለከት ማህበሮቹ ለስራ ተሰማርተው ያገኙትን ትርፍ ሁሉ አጠቃሎ መወሰን ሲገባው ማህበሮች በተቋቋሙበት ጊዜ በተደረገው መነሻ ይካተታል መጠን ላይ መወሰኑ አግባብ አለመሆኑን እንዲሁም በልዩ ልዩ በባንኮች በእነዚሁ ተጠሪዎች ስም አንፃር ይገኛል የተባለውን ሀብት መጠን አስመልክቶ ፍ/ቤቱ ገንዘብ ስለመኖሩ በጠየቀበት ጊዜ በባንኮች ተቀምጦ ተገኝቷል የተባለውን የገንዘብ መጠን ሳይሆን በትዳር በነበሩበት ጊዜ አንደኛዉ ወገን ብቻ በማውጣት ለግል ጥቅም ተጠቅሞበታል ከሚያሰኝ በቀር ለጋራ ጥቅም እንደዋለ አያስቀጥርም በማለት መነሻ ሊሆን ከሚችለው ጊዜ ጋር በማስተያየት በባንኮች ካላቸው ሂሳብ እንቅስቃሴ  በመነሳት መሠረት የሚገባዉ መሆኑን ጠቅሰን በዚሁ መሠረት እራሱ ይግባኝ በከካሽ ፍርድ ቤት ጉዳዮን ተመልክተ የገንዘቡን መጠን በፍርዱ የውሣኔ ክፍፍል በተገለፀው አኳኋን ከፍ አድርጎ በሚሻሻል መወሰን ፤

 

በሸር ድርሻ ላይ የተወሰነውን የድርሻ መጠንን ከላይ በተመለከተው መሠረት ከውሳነ በኃላ የክፍፍል ማስረጃን በሚመለከት 1ኛ መልሰ ሰጭ በሀብቱም ማህበሮች የተወሰነላቸውን የአክስዮን ድርሻ ለተቻለ እና ተጠሪዎች የሚስማሙ ከሆነ በአባልነት እንዲቀጥሉ ይህ ካልተቻለ ተሽጦ የሽያጩን ድርሻ ይከፈላቸው የአከስዮኖች አሻሻጭም በንግድ ህግ አንቀጽ 523 እና ተከታዮች ድንጋጌዎች እንደዚሁም የሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ.57288 በሰጠው የህግ ትርጉም መሠረት ሆኖ ድርሻቸው እንዲሰጣቸውና እንዲሁም በቤት ቁጥር 2545 ውስጥ/ የተሰጠውን ዕቃ በሚመለከት ቀርቧል በተባለው የወንጀል ክስ ምርመራ ውጠት መሠረት የአሁኑ አመልካች ጥያቄ የማቅርብ መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን ከዚህ በላይ ከተገለፁት በቀር ሥማቸው በሥር ፍ/ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ የፀና መሆኑን ለመግለፅ በሥር ፍ/ቤት የተሰጠውን ውሣኔ በማሻሻል የወሰነ መሆኑን ከፍርዱ ግልባጭ ተረድተናል ፡፡


የአሁን አመልካች በዚህ የሰበር ሰሚ ችሎት ሊታረም ይገባል በማለት ለቅሬታቸው መሠረት ያደረጉት የቤት ቁጥር 2545 የሆነው ቤት የባልና ሚስት የጋራ ሀብት ነው ወይስ የአሁን 3ኛ ተጠሪ የሚለውን ለይቶ በመወሰን ረገድ፤እንዲሁም በሥር ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት ውሣኔ የተረጋገጠባቸውን የአክስዮን ድርሻዎ የክፍፍሉን መንገድ በሚመለከት የአክስዮን ድርሻዎች በሚገኙበት ማህበር በአባልነት እንድቀጥል በማድረግ መወሰን ስገባው ማህበሩ ለተስማማ በሚል ተገልፆ የህግ መሠረት የለውም ለሚሉት መወሰኑ ነጥቦች ላይ ፡፡

 

ተጠሪዎችም በበኩላቸው ክርክር በሚመለከታቸው ክርከር አንፃር በሥር ፍ/ቤቶች የተሰጠው ዳኝነት መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት አይደለም የሚሉበትን ምክንያት በመጥቀስ ተከራክረዋል፡፡

 

እንግዲህ የጉዳዮ አነሳስ፤የክርክሩ ይዘትና የሥር ፍ/ቤቶች በየደረጃው የሰጡት ዳኝነት ፤የዚህን ዳኝነት አግባብነት በሚመለከት ወገኖች በዚህ ሰበር ችሎት ያቀረቡት ክርክር በይዘት ደረጃ ከላይ ከፍ ሲል ባጭር ባጭሩ የተመለከተው ሲሆን ፤እኛም ጉዳዮን እንደሚከተለው መርምረናል ፡፡ ተመልክተናል ፡፡

 

ጉዳዮን እንደመረመርነውም በቤት ቁጥር 2545 የተመለከተውን ቤት አስመልከቶ የአሁን አመልካች ከሥር ፍ/ቤት ጀምሮ ለክርክራቸው መሠረት ያደረጉት ንብረቱ በሽያጭ ወደ አሁን 3ኛ ተጠሪ የተላለፈው ፍ/ቤቱ በዚሁ ንብረት ላይ ዕግድ ከሰጡበት በኃላ የፍ/ቤቱ ዕግድ ተጥሶ ስለሆነ የሽያጭ ተግባሩ ዋጋ አልባ ስለሆነ ሊፈርስ ይገባል የሚለውን አንደኛው የክርክር ነጥብ ሲሆን የዚህኑ ክርክር አግባብነት ለዚሁ ጉዳዮ በሥር ፍ/ቤቶች በነበረው የክርክር ሂደት በማስረጃ ከተረጋገጠው የፍሬ ነገር ጉዳይ በመነሳት ተመልክተናል ፡፡

 

የአሁን አመልካች ለዚህ የሰበር ጉዳይ መነሻ የሆነውን ክስ ከቀረቡ በኃላ የክርክሩ ውጤት እስክታወቅ በሚል ይኽው ቤት በማናቸውም መንገድ ቢሆን ወደ ሶስተኛ ወገን እንዳይተላለፍ የዕግድ ትእዛዝ የሰጡት የካቲት 16 ቀን 2003 ዓ.ም መሆኑና ይኽው ቤት በአሁን 1ኛ ተጠሪ አማካኝነት በዓይነት በመወጫነት ወደ ጂ.ኤስ.ኤ ጀኔራል ትሬድንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የገባውና ስመ ሀብትነቱም ወደ ዚሁ ማህበር ስም የተላለፈው ይኽው የወሰነበት የዕግድ ትእዛዝ ከመስጠቱ በፊት ስለመሆኑ በሥር ፍ/ቤት የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ የአንድ ንብረት ባለሀብት ማን ነው የሚለው የሚወሰነው ደግሞ ንብረት ከአንዱ ወደ ሌላው ለማስተላለፍ የሚያስችለው እንደ ሽያጭ ስጦታ ወዘተ የመሳሰሉት ህጋዊ ተግባሮች በህግ ፊት በሚፀና አኳኋን ተፈፅመው እንደሆነ እና በዚሁ አኳኋን በተፈፀመው ህጋዊ ተግባር የተነሣ በንብረቱ ላይ የባለቤትነት መብት ያገኘ ሰው ንብረቱን ካስተላለፈዉ ተፈጥሯዊም ሆነ የህግ ሰው ባሻገር ማናቸውንም 3ኛ ወገን ለመመለስ የሚያስችለውን የስመ ሀብት ዝውውር ሥርዓት ሁሉ ታከናውኖ እንደሆነ በፍ/ብ/ህግ ቁጥር


1678 ፣1731፣1184፣1195 ተደንግጓል፡፡ አሁን የተያዘውን ጉዳይ ከእነዚህ ድንጋጌዎች አንፃር ስነየው ክርክር ያስነሰው ንብረት በ1ኛ ተጠሪ እና ጀ አስ ኤ ጀኔራል ትሬዲንግ መካከል በተደረገ ስምምነት መሠረት ይኽው ንብረት በዓይነት በመወሰኑ ወደ ከማህበሩ ገብቶ፤ ማህበሩ በዚሁ ንብነት ላይ መብትና ግዴታ ያቋቋመ ሲሆን ከዚሁ ንብረት ወደ ማህበሩ መግበት የተነሰ ለአስተላለፈውም ግዴታ ፈጥሮለታል ይህ በህግ የተፈቀደ ንብረት ሊተላለፍ የሚችለበት አንዱ ህጋዊ ተግበር ሲሆን ማህበሩ በዚሁ ንብረት ላይ የእኔ በይ በመጣ ለመመለስ ዋስትና የሆነውን የስመ ሀብት ዝውውር ሥርዓት ሁሉ ፈፅሟ፡፡ በዚህም መሠረት የዚሁ ንብረት የበላቤትነት መብት ያለው ይኽው ማህበር እንጂ ሌላ ማናቸውም ወገን ሊሆን አይችልም ይህን በንብረት ላይ ያለን የበለሀብትነት መብት ማህበሩ ያቋቋመው ፍ/ቤቱ በንብረቱ ላይ የዕግድ ትዕዛዝ ከመስጠቱ በፊት ነው ከዚህ በንብረቱ ላይ የበለቤትነት መብት ከቋቋመ በኃላ በዚህ በህግ ከቋቋመው ላይ የበለቤትናት መብቱ ተጠብቆም በንብረቱ ላይ የማዘዝ ወደ ሌላ 3ኛ ወገን የመስተልለፍ መብት ያለው ሲሆን ሌላ ማየናቸውም 3ኛ ወገን ይህንኑ ንብረት ለሚመለከት ከመህበሩ ጋር በሚያደረገው ህጋዊ ተግበር ወደ እራሱ ያዛወረው ከሆነ ንብረቱን ለማዘወር መብትና ስልጣን ከለው ወገን ያገኘ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ለመለየት ማህበር ንብረቱን በሸጠበት ጊዜ በንብረቱ ላይ የተመለከተውን ስመ ሀብትነት ምዝገባ የሚከተል እንጂ 3ኛ ወገን ከማህበሩ ጋር ግብይት የፈፀመበት ጊዜ ሊሆን አይችልም ከዚህ በላይ ንብረት ከንደኛው ወገን ወደ ሌላው ሊተላለፍ የሚችልበትን መንገድ በሚመለከት በተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተቀመጡት ሁለት ቋሚ መሟያዎች ማናቸውም በንብረት ላይ ሊኖር የሚችለው ግብዓት በህግ ዋስትና ተሰጥቶት በህ/ሰብ ደረጃ ያለስጋት የሠለጠ ኢኮኒሚያዊ ግንኙት ለመፍጠር እንዲያስችል ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የአሁን አመልካች የፍ/ቤቱ የዕግድ ትዕዛዝ ከተለለፈ በኃላ 3ኛው ተጠሪ ከማህበሩ ጋር የሽያጭ ውል ያደረገበትን ጊዜ ተንተርሰው የሚያቀረቡት ክርክር የህግ መሠረት ያለው ሆኖ አላገኘነውም ፡፡

 

ከዚህም በቀር የማይንቀሳቀስ ንብረት በዓይነት ለመውጫ ወደ አክሲሆን ማህበር ወይም ወደ ኩባንያ ስለመዘወሩ በመመስረቻ ፅሑፍ ሰፍሮና በዚህ መስረጃ መዝገብ ጽ/ቤት ተመዝግቦ በማንቀሰቀስ ንብረት በመዝገብ ውስጥ መመዝገቡ ከተረጋገጠ የ3ኛ ወገኖችን ላይ ለመመለስ የሚያስችለው ሥርዓት መሟለቱን እንደሚያመለክት ይህ ለሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ ቀርቦ ተመሰሰይ በሆነው በሰበር መ/ቁ.. 27869 ትርጉም የሰጠበት ጉዳይ በመሆኑም ጭምር ከዕግድ ትዕዛዝ ጋር በተያየዘ የአሁን አመልካች የሚያቀርብበት ክርክር በስር ፍ/ቤቶች የተሰጠው ዳኝነት መሠረተዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት መሆኑን የሚያመለክት ህጋዊ መሰረት የለው ክርክር አይደለም ሌላውና ይህንኑ በቤት ቁጥር 2545 የተመለከተውን ቤት  አስመልክቶ የአሁን አመልካች ያቀረቡት ክርክር በዋጅ ቁጥር 2/3/92 ስለጋራ የበልና ሚስት ሀብት አስተዳደርና ጥበቃ በህጉ የተቀመጠውን  የተጋቢዎች የጋራ ስምምነትን አስፈላጊነት በመጥቀስ ነው፡፡


የጋራ ሃብት የሆነን ንብረት አንደኛው ተጋቢ ያለ ሌላኛው ተጋቢ ስምምነት ለሌላ ሶስተኛ ወገን በሽያጭ ማስተላለፍ እንደማይችል በዚሁ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 68 የተደነገገ ሲሆን፤ ይህ ድንጋጌ በይዘቱ የጋራ በሆነ ንብረት ላይ ተጋቢዎች እኩል መብት ያላቸው መሆኑን በህገ- መንግስቱ አንቀጽ 34(1) የተመለከተውን ህገ-መግስታዊ ድንጋጌ ተከትሎ የተደነገገ ሲሆን፤ በሌላ በኩል በአገር በማህበረሰብ ውስጥ ንብረትን አስመልክቶ የሚደረገው ግብይት ያለማነቆ በሰለጠ አኳኋን እንዲፈጸም ካልተደረገ በአገር የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ሊያደርስ የሚችለውን እንቅፋት በማየት ይህ ከላይ የተመከተው የጋራ ስምምነት አስፈላጊነት በሁኔታ ላይ እንዲመረኮዝ በማስፈለጉ ተከታይ በሆነው አንቀጽ 69 እንደተመለከተው አንደኛው ተጋቢ ያለፈቃዱ ንብረቱ በአንደኛው ተጋቢ ብቻ መሸጡን በተረዳ ጊዜ ይህ የሽያጭ ተግባር በህጉ የተሰጠውን መብት የጣሰ መሆኑን መነሻ አድርጎ በክስ አማካኝነት ማስፈረስ እንደሚቻል፤ ይህንኑ የማስፈረስ ተግባሩን ካልተጠቀመ፤ ወይም በህጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የማስፈረስ ጥያቄው ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ካልቀረበ ግን አንደኛው ተጋቢ ብቻውን የፈጸመው ህጋዊ ተግባር እንደጸና እንደሚቀር እንጂ የጋራ ስምምነት ባለመኖሩ ምክንያት ብቻ ንብረቱ የተላለፈበትን ግብይት ወይም የሽያጭ ውል በዘፈቀደ በማናቸውም ጊዜ መቃወም እንደማይቻል ተደንግጓል፡፡ ስለሆነም የስር ፍ/ቤቶች በዚህ ረገድ የሰጡት ዳኝነት የህጉን ትክክለኛ አፈጻጸም የተከተለ እንጂ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመ አይደለም፡፡

 

የአሁን አመልካችም ይህንኑ ተገንዝበው ክርክራቸው በይግባኝ ደረጃ ለደረሰበት ጊዜ በዚሁ ስርዓት መሰረት በንብረት ላይ ያላቸውን መብታቸውን ለማስከበር ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ክስ አቅርበው በክርክር ላይ የሚገኙ መሆኑን የገለጹ በመሆኑና ይህ ችሎም ለትክክለኛ ፍርድ አሰጣጥ ይህንኑ የተባለውን በመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የቀረበውን የኮ/መ/ቁ. 194776 የሆነውን መዝገብም አስቀርበን እንደተመከትነው ጥያቄውን በዚያው አግባብ ማቅረባቸውን ተገንዝበናል፡፡ ይኸው ፍ/ቤትም ጉዳዩን ለጊዜው የዘጋው የፌዴራል ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት በኮ/መ/ቁ. 125895 የቀረበለትን የይግባኝ ጉዳይ መርምሮ የመጨረሻ ዳኝነት እስኪሰጥበት ጊዜ  ድረስ በማገዱ ምክንያት በመሆኑና ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ዳኝነት የሰጠበት ጉዳይ ስለሆነ የስር ፍ/ቤቶች በፍርዳቸው ላይ እንደገለጹት መብታቸውን ከሚያስከብሩ በቀር በዚህ የጋራ ንብረት መሆኑ ተረጋግጦ የጋራ ሃብትን ለማከፋፈል እንዲቻል በቀረበው መዝገብ ላይ ወደ ሶስተኛ ወገን በሽያጭ አማካኝነት ተላልፎ የባልና ሚስት የጋራ ሃብት መሆኑ ያልተረጋገጠውን የቤት ቁጥር 2545 እንደጋራ ሃብት ሊቆጠር ይገባል በማለት የሚያቀ ርቡት ክርክር ተቀባይነት ያለውም አይደለም፡፡

 

ሌላውና ለዚህ የሰበር ጉዳይ የክርክር ምክንያት የሆነው ለአሁን አመልካች ይግባኝ ሰሚ ከፍተኛው  ፍ/ቤት  አሻሽሎ  በወሰነላቸው  የአክሲዮን  ሼር  ድርሻ  ላይ  ያላቸውን     ሀብት


የሚያገኙበትን ተጠቃሚ የሚሆንቨትን መንገድ ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሚስማማ ከሆነ በአባልነት እንዲቀጥሉ ይህ ካልሆነም ተሽጦ የሸያጭ ድርሻ እንዲያገኙ በማለት በንግድ ህግ ቁጥር 523 እና ተከታዮቹ የተመለከተውን መሠረት በማድረግና በሰበር ሰሚው ችሎት በሰበር መ/ቁ.57288 የተሰጠውን ትዕዛዝ በመከተል የሰጠውን ዳኝነት አግባብነቱን አስመልክቶ ግራ ቀኙ ክርክር ያደረጉበት ጉዳይ ነው፡፡

 

ይህንንም ጉዳይ እንደተመለከትነው በማናቸውም ምክንያት በፍ/ቤት በሚሰጥ  ፍርድ የሚረጋገጠው መብት ከተብ ወይም ከውል የመነጨውን መብት መኖርና አለመኖር አስመልክቶ እንዲህጉ አነጋገር ለማስረዳት የቀረበውን ክርክርና ክርክሩን አነጋገር ለማስረዳት የቀረበውን ክርክርና ክርክርን ለማስረዳት የቀረበውን መብት ወደ ተግባር ይህንኑ ከህግ እንዲያስችል ለመብት ምንጭ የሆነውን ህግ መሠረት በማድረግ ነው፡፡

 

ከዚህም አንፃር ጉዳዩን አግባብነት ካለው ህግ ጋር ተገናዝቦ ሊታይ የሚገባው ነው፡፡

 

አግባብነት ካላቸው ህጎች አንዱ ይኸው የአክቢዮን ድርሻ ግራ ቀኙ በጋብቻ ዘን በነበሩበት ጊዜ የተፈራ የጋራ ሀብት እንደመሆኑ መጠን በሀብቱ የባለእኩልነት ድርሻቸውን የሚቃረጋግጠው አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጽ 62 አንዱ ሲሆን እንዲሁም ከዚሁ የጋራ ሀብት ነው፡፡ ከተባለው የሀብት ዓይነት አንፃር ሲታይ ደግሞ የዚህ የጋራ ሀብት የክፍፍል ሁኔታ የሀብቱን ጉዳይ ምክንያት በማድረግ በሚደነግገው በንግድ ህጉ አንቀጽ 523 የተመለከተው ድንጋጌ ደግሞ ሌላው ነው፡፡ ስለሆነም የዚህኑ ክፍፍል ሥርዓት የሚደረግበትን መንገድ በሚመለከት የሥር ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት በንግድ ህጉ አንቀጽ 523 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ መሠረት ማድረግ የሚያነቀፍ አይደለም፡፡ ሆኖም ይህንኑ ድንጋጌ እንደሙሉ ይዘቱ አይነት ተፈፃሚ በማድረግ ስለሆነም የአሁኑ አመልካች በፍርድ በተረጋገጠላቸው የአክሲዮን ድርሻ ቫት መብት ላይ ከንግድ ህጉ አንቀጽ 523 አንፃር አየቶ መብቱን ለማረጋገጥ መነሻ ለሆኑ ከሚገባቸው የህጉ ክልሎች መካከል በንግድ ህጉ አንቀጽ 523/2/ እንደተመለከተው የአክሲዮን ማህበር መመሥረቻ ፅሑፍ የይዙቱ የአሁን አመልካች በማህበሩ አባልነት ተካተው በአባልነት ይህንኑ ለፍርድ በተረጋገጡባቸው የአክሲዮን ድርሻ ሀብት መገልገል የሚቻሉ መሆኑንና አለመሆኑን አስመልክቶ ምን እንደሚል ከመመስረቻ ፅሑፍ ጋር አገናዝቦ ከታየ በኋላ ሊታይ የሚገባው እንጂ ሆና እያለ ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሰጠው ዳኝነት በዚህ ረገድ የተባለ ሆኖ አላገኘነውም ስለሆነም በዚሁ የነግድ ህግ ቁጥር 523/2/ ድንጋጌ ተትክከለኛ አፈፃፀሙን ተከትሎ ፍርድ በመስጠት  ረገድ የታየው ጉድለት ሊታረም የሚገባው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

 

በዚህ ሁሉ ምክንያት የሚከተለውን ውሣኔ ሰጥተናል፡


 ው ሣ ኔ

 

1. የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በኮ/መ/ቁ.61875በቀን 13/10/2004 ዓ5ም የሰጠውን ፍርድ እንዲሁም ይግባኝ ሰሚው ከፍተኛ ፍ/ቤት በኮ/መ/ቁ12559 ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም የሰጠውን ፍርድ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 325/1/ መሠረት አሻሽለን ወስነናል፡፡

2. በን/ስ/ላ/ከተማ ወረዳ 03 ክልል ውስጥ በመ/ቁጥር 2545 ተመዝገቦ የሚታወቀው  ቤት ላይ የባለቤትነት መብት ያለው የአሁን 3ኛ ተጠሪ አቶ ሐገስ አብዱራህማን ናቸው መባሉ በአግባቡ ነው ብለናል፡፡

3. ለአሁን አመልካች በፍርድ በተረጋገጡላቸው የአክሲዮን ድርሻና መጠን ላይ ባላዠው የሀብት መብት ላይ መገልገል የሚቻልበት ማበህበሩ አባልነት ተካተው በአባልነት ነው ወይስ በአባልነት መገልገሉ የሚቻሉበት ህጋዊ ምክንያት ታይቶ በሐራጁ ተሽጦ ይህንኑ ሀብት እንደያገኙት ነው?የሚባለው ጭብጥ ከማህበሩ መመስረቻ ፅሑፍ ይዘት እና ከንግድ ህጉ አንቀጽ 523/2/ አንፃር ታይቶ ይወሰልን ዘንድ ብቻ መዝገቡን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁ.343/1/ መሠረት ወደ ሥር ፈ/ቤት መልሰናል፡፡

4. የዚህ ክርከር ውጤት እሰኪታወቅ ድረስ በሚል በዚህ የስር መዝገብ ቁጥር 103721 ተሰጥቶ የነበረው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይፃፍ፡፡

5. የዚህ የሰበር ክርክር ጉዳይ ስላስከተው ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸው ይቻሉ፡፡ ብለናል፡፡

መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል፡፡

የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት፡፡

 

 

መ/ተ