የመጀመሪያ ሚስት በንብረትዋ ላይ ስምምነት ባላደረገችበት ፤ባል ሁለተኛ ሚስት ሲያገባ መቃወሚያ አላቀረበችም በማለት በንብረትዋ ላይም ስምምነት አድርጋለች በማለት በመደምደም ፤ሁለተኛ ሚስት እኩል እንድትካፈል በማለት የሚሰጥ ውሳኔ ህጋዊ ስላለመሆኑ
Download Cassation Decision
የባልና ሚስት የጋራ ንብረት ነው የተባለ ንብረትን አፈፃፀምን በተመለከተ የንብረቱ ሕጋዊነት ላይ የሚመለከተው አስተዳደር አካል አግባብ ያለው ውሣኔ እስኪሰጥ ድረስ መሸጥ መለወጥ ባይቻልም ባለበት ሁኔታ የግራ ቀኙን እኩል ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ አግባብ በጋራ የሚያስተዳድሩበት ወይም ተከፋፍለው የሚጠቀሙበት ወይም አከራይተው ጥቅሙን እኩል የሚከፋፈሉበት ሁኔታ መመቻቸት ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ 386/2/
አ ንድ የንግድ ቤት በኪራይ የተሰጠው በትዳር ግንኙነት ወይም በጋብቻ ውስጥ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ የንግድ ፈቃድ የተሰጠው ከትዳር ግንኙነት በፊት መሆኑ ብቻ የንግድ ሱቅ ከጋብቻ በፊት የተገኘ የግል ንብረት ነው ለማለት የማያስችል ስለመሆኑ፣
ባ ል እና ሚስት በጋራ ሲጠቀሙበት የነበረ መሬት ጋብቻው በአንደኛው ተጋቢ ሞት የተቋረጠ ቢሆንም ሌላኛው ተጋቢ በሌላ ህጋዊ ምክንያት መብቱ እስካልተቋረጠ ድረስ ይዞታው በስሙ ተመዝግቦ ደብተር ለማግኘት እና በይዞታው ለመጠቀም የሚችል ስለመሆኑ፣ ሴቶች መሬትን በመጠቀም፤በማስተላለፍ፤በማስተዳደርና በመቆጣጠር ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት ያላቸዉ ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕ/መ አንቀጽ 35/7/፣ የኦሮሚያ የገጠር መሬት አዋጅ ቁ. 130/99 አንቀጽ 6/3/ እና ደንብ ቁጥር 151/2005 አንቀጽ 15
የ ባልና ሚስት ንብረት ክፍፍልን በተመለከተ ለአፈፃፀም የቀረበ አከራካሪ የሆነ ቤት ሊካፈልም ሆነ ሊሸጥ የማይችል ሲሆን ሊካፈል የሚችለው በፕሮፖርሽን / በተነጻጻሪ ካርታ / ነው በማለት ባለሙያ አስተያየት በተሰጠበት ሁኔታ በዚሁ አግባብ ክፍፍሉ ሲደረግ የበለጠ ይዞታ የደረሰው ወገን ለሌላው ወገን ግምቱን እንዲከፍል በማድረግ መፈፀም የሚገባው እንጂ በፍርዱ በተቀመጠው ሌላ አማራጭ መሠረት ክፍፍሉ እንዲፈጸም ማድረግ የማይገባ ስለመሆኑ፡- የተሻሻለው የፌዴራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 91(1)እና(2)
የባሌና ሚስት ፌቺ ተፇጽሞ የንብረት ክፌፌሌ እስከሚዯረግ ዴረስ በጋብቻ ውስጥ የተፇራ ንብረትም ሆነ ከዚህ ንብረት የሚገኝ ገቢ የጋራ ሆኖ የሚቆይ ስሇመሆኑየተሻሻሇው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጽ 89
Download decision
የኮንደምኒየም ቤት እጣ ከጋብቻ በፊት ወጥቶ የኮንዶሚኒየም ቤቱ የሽያጭ ውል የተፈረመው ወይም የተደረገው በጋብቻ ውስጥ በሆነበት ሁኔታ ለቤቱ የተከፈለው ገንዘብ ምንጭ የሆነው ወገን የግሉ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር ቤቱ የአንደኛው ተጋቢ የግል ንብረት ነው ሊባል የሚችልበት ህጋዊ ምክንያት የሌለ ስለመሆኑ የፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 255
Download
በባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ክርክር ወቅት ድብቅ የጦር መሳሪያ መኖሩ እስከተረጋገጠ ድረስ በሕግ አግባብ ስልጣን ባለዉ አካል አለመመዝገቡ መሳሪያዉ የለም የሚያስብል ሳይሆን የኢኮኖሚ ጥቅም ያለዉ እና ባልና ሚስት በትዳር እያሉ ያፈሩት እስከሆነ ድረስ ከሚመለከተዉ አካል ተመዝግቦ መሳሪያዉን ለመያዝ ፈቃድ አለመሰጠቱ፣ የተጋቢዎቹ የጋራ ሀብት እንዳይሆን የማያደርገዉ ስለመሆኑ የአማራ ክልል የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 79/1995 አንቀጽ 73 (1) እና 101
ጋብቻ በፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ በንብረት ክርክር ወቅት የግል ዕዳ ነዉ ተብሎ ውሳኔ ያገኘ ዕዳ ፍ/ቤት ቀርቦ ባልተለወጠበት ሁኔታ በባለዕዳው ተጋቢ በኩል ለመጣው እዳ ሌላኛው ተጋቢ ተጠያቂነት የሌለበት ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 34 (1)፣ የፌደራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 57፣ 70፣ 71፣ 89 እና 93
የፍ/ብ/ህ/ቁ. 658 ተጋቢ ወገን ከሦስተኛ ወገን ጋር ያደረገውን ውል ለማፍረስ ምክንያት ስላለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 658, 686
Cassation Decision no. 28663
ከጋብቻ በፊት የግል የነበረን ንብረት መነሻ በማድረግ በጋብቻ ጊዜ በግብይት የተገኘ ንብረት የግል ሆኖ ሊቀጥል የሚችለው በፍ/ቤት ቀርቦ የፀደቀ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 58(2) 57 62(2)
የአንደኛው ተጋቢ ስምምነት ሣይኖር የጋራ የሆነ የማይንቀሣቀስ ንብረት በሌለኛው ተጋቢ የተሸጠ እንደሆን ስምምነቱን ያልሰጠው ተጋቢ ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ 6 ወር ውስጥ እንዲሁም በማናቸውም ሁኔታ ደግሞ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ ለመጠየት ስለመቻሉ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 69(2)
በጋብቻ ውል ላይ ባልና ሚስት “መተዳደሪያችን” ነው በሚል ያመለከቷቸው ንብረቶች የጋራ ንብረት ተደርገው የሚቆጠሩ ስለመሆናቸው
ጋብቻ ሳይፈርስ የትዳር ግንኙነቱን ትቶ የሄደ ተጋቢ ጋብቻውን ትቶ በሄደበት ወቅት የተፈራን ንብረት የጋብቻ ውጤት ነው በማለት የክፍያ ጥያቄ ሲያቀርብ በጋብቻ ወቅት የተፈራን ንብረት የጋራ ይሆናል በሚለው የህግ ግምት ተጠቃሚ ሊሆን የማይገባ ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 40/1/
ከጋብቻ በፊት በአንደኛው ተጋቢ የተፈራ ቤት በጋብቻ ወቅት እድሳት የተካሄደለት መሆኑ ብቻ ንብረቱን የባልና ሚስቱ የጋራ ሃብት የማያደርገው ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥ. 213/92 አንቀጽ 42/1/, 57
አንድ ወንድ ሁለት ሚስቶች ጋር ተጋብቶ በሚገኝ ጊዜ የንብረት ክፍፍል ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የፌዴራል የተሻቫለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ. 213/92 አንቀጽ 102(1),86(1),62(1),63(1) የአማራ ብ/ክ/መ/የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 113(1),97(1),73(1),74(1)
የኮንዶሚንየም ቤት ለማግኘት የተደረገ ምዝገባ ከጋብቻ በፊት ቢሆንም ዕጣ የወጣው ጋብቻ ፀንቶ ባለበት ጊዜ ከሆነ ተጋቢዎቹ የመካፈል መብት የሚያገኙ ስለመሆኑ Download Cassation Decision
በሁለት የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ቤቶች የጋብቻ ፍቺን ተከትሎ ለባልና ሚስት ሊከፋፈሉ የሚችሉበት አግባብ
ባል ሁለት ሚስቶችን በአንድ ጊዜ አግብቶ የሚኖር በሆነ ጊዜ በመካከላቸው የሚፈራ ንብረት ለተጋቢዎቹ ሊከፋፈል የሚችልበት አግባብ ሚስቶች ጋብቻ እንደተፈፀመ ከሚቆጠርበት ጊዜ ጀምሮ ከባል ጋር ያፈሩትን ሀብት ብቻ መካፈል ስለመቻላቸው
በባልና ሚስት የጋራ ንብረት ላይ የተደረገ የሽያጭ ውል በሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ አለመፍረሱ ስለሚያስከትለው ውጤት
Page 2 of 3