 የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የሚደረግ የሽያጭ ዉል ንብረቱ በተመዘገበበት መዝገብ ላይ መመዝገብ እንዳለበት ህጉ ሲደነግግ ገዥዉ ዉሉ እንዲመዘገብ በሚመለከተዉ አካል ዘንድ ሲቀርብ ንብረቱ በሻጭ ስም መመዝገብ አለመመዝገቡን ወይም ሻጩ ዉሉን ለማድረግ ህጋዊ መብት ያለዉ መሆን አለመሆኑን ብቻ ሳይሆን በንብረቱ ላይ ዕዳ እና እገዳ ያለበት መሆን ያለመሆኑንም ለማጣራት ዕድል ያገኛል በሚል በመሆኑ ማንኛዉም ጠንቃቃ ገዥ ዉል ሲዋዋል ተገቢዉን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የሚጠበቅበት ስለመሆኑ 

የባልና ሚስት የጋራ ንብረት የሆነ ቤት ያለ አንደኛው ተጋቢ ፊቃድና ስምምነት ለሦስተኛ ወገን እንዳይተላለፍ በፍርድ ቤት አስቀድሞ እግድ የተሰጠበት ስለመሆኑ ንብረቱ በተመዘገበበት መዝገብ ላይ ተረጋግጦ እያለ፣ የሽያጭ ዉሉም መመዝገቡም ሆነ የሚመለከተዉ አካል ዉሉን ሲመዘግብ ወይም ሲያረጋግጥ ተገቢዉን ጥንቃቄ ሳያደርግ ቤት በሽያጭ በመተላለፉ የገዛ ሰው እንደ አንድ ጠንቃቃ ገዥ ማድረግ የሚገባዉን ጥንቃቄ አለማድረጉን የሚያሳይና አስቀድሞ የተቋቋመ የሌላ ሰዉ መብትና ጥቅም ያለበትን የማይንቀሳቀስ ንብረት በመግዛት የተደረገ ዉል ጸንቶ የማይቀጥል ስለመሆኑ  
የፍትሐ ብሔር ህግ አንቀጽ 1543-1566 እና 1185  

Download